በስድስት ክልሎች የሚገኙ 64 ለፓርላማና 133 ለከልል ምክር ቤት የሚመርጡ የምርጫ ክልሎች ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም. ሳይሆን ጳጉሜ 1 ቀን 2013 ዓ.ም. ድምጽ እንደሚሰጥባቸው ታወቀ፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባሰራጨው ጳጉሜ 1 ምርጫ የሚደረግባቸው የምርጫ ክልሎች ዝርዝር. በአማራ 10፣ በአፋር 2፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ 4፣ በሐረሪ 2፣ በኦሮሚያ 7፣ በደቡብ ክልል 16፣ እንዲሁም በሶማሊ 23 ሲሆኑ፣ 133 የክልል ምክረ ቤት የምርጫ ክልሎችም በተመሳሳይ ጳጉሜ 1 ይመርጣሉ፡፡ በዚህም መሠረት በአማራ 9፣ በአፋር 7፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ 13፣ በሐረሪ 3፣ በኦሮሚያ 7፣ በደቡብ ክልል 22፣ እንዲሁም በሶማሊ ክልል 72 የክልል የምርጫ ክልሎች ጳጉሜ 1 ቀን 2013 ዓ.ም. ድምጽ ይሰጣሉ።
ምንጭ – ሪፖርተር